ድጋፍ እና እገዛን በሚመለከት ፦
– ድርጅቱ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከላከል እና መቆጣጠርን በተመለከት በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሆነ ገልጿል።
– ድርጅቱ በሚገኝባቸው ወረዳዎች እና አጎራባች ወረዳዎች በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ያሉ ለ400 ሰዎች እገዛ እና ድጋፍ አድርጋል።
– ተቋሙ ለሚያሳድጋቸው 15 ወላጅ አልባ ህፃናት በየወሩ የሚያደርገው ድጋፍ እንደተጠበቀ ሆኖ የዘይትና የዱቄት ድጋፍ አድርጋል።
የእርድ እና የስጋ ስርጭት አገልግሎትን በሚመለከት ፦
– የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ለመከላከል የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ ነው። ቀዳሚ የነበረው ሰራተኞችን ማሰልጠን፣ ግንዛቤ መስጠት፣ በተለይም ሚኒ ሚዲያውን በመጠቀም ተሰርቷል።
– ድርጅቱ የሙቀት መለኪያ አስገብቶ ሰራተኞች ሲገቡ ሙቀታቸው እንዲለካ፣ የእጅ ጋንት፣ ሳኒታይዘር እና ሌሎች የንፅህና መጠበቂየዎች እንዲሰጥ ተደርጓል።
– ተሽከርካሪዎች ከከተማ ሲመጡ የኬሚካል ርጭት እየተደረገ ይገኛል። ኬሚካል ርጭቱ ሊያገኛቸው የማይችሉ የመኪና ክፍል (በተለይም የጎማ ክፍል) ‘ማለፊያ ቦታ’ ተሰርቶ መኪናዎች ጎማቸው በኬሚካል እንዲፀዳ እየተደረገ ነው።
– እንስሳት ሲገቡ ከፍተኛ ጥንቃቄ ተደርጎ እየተሰራ ነው፣ የእርድ ክፍሎች ሴራሚክ ተደርገዋል፤ ክፍሎቹ ፅዳታቸውን በየጊዜው ይጠበቃል።